Friday, January 30, 2015

መንግስት ከምርጫው በፊት አፈናውን ያቆማል የሚለው ተስፋ መሟጠጡን ሂውማን ራይተስ ወች አስታወቀ

ድርጅቱ ባወጣው የ2014 አለማቀፍ የሰብአዊ መብት አያያዝ ሪፖርት ላይ እንደጠቀሰው መንግስት ጋዜጠኞችን፣ ጸሃፊዎችን እና  የተቃዋሚ ፓርቲ ደጋፊዎችን እንደፈለገ  ያስራል፣ በሰላም ተቃውሞአቸውን ለመግለጽ በወጡ ዜጎች ላይ ፖሊስ የሃይል እርምጃ ይወስዳል፤ እንዲሁም ለማፈኛነት እየዋሉ ያሉትን በአለማቀፍ ማህበረሰብ ዘንድ የተወገዙትን አዋጆችን ለመለወጥ ምንም ምልክት አላሳየም ብሎአል።
ባለፈው አመት የኢትዮጵያ መንግስት ማንኛውንም ተቃውሞ ለማፈን መሞከሩን የገለጹት የሂውማን ራይትስ ወች የአፍሪካ ምክትል ዳይሬክተር ሌስሌ ሌፍኮው፣ ጋዜጠኞችና ተቃዋሚዎች ከሁሉም በባሰ እንደተሰቃዩና ከመጪው ምርጫ በፊት ሁኔታዎች ይሻሻላሉ የሚለው ተስፋ ሙሉ በሙሉ እንደተዳፈነ ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ እየፈጸመች ያለችው አስከፊ የሰብአዊ መብት ጥሰትን የለጋሽ አጋራትን አለመተቸታቸውን  ሂውማን ራይትስ ወች በሪፖርቱ አመልክቷል።ሰማያዊ ፓርቲ የተቃውሞ ሰልፎችን እንዳያደረግ መከልከሉ፣ በኦሮምያ ክልል በሚያዚያና ግንቦት ወሮች የጸጥታ ሃይሎች ከፍተኛ ጉዳት ማድረሳቸው፣ የግንቦት7 ዋና ጻሀፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ህገወጥ በሆነ መንገድ የመን ውስጥ ተይዘው መሰጠታቸውና የታሰሩበት ቦታ አለመታወቁንም ገልጿል።
ዞን 9 እየተባሉ የሚጠሩ ጸሃፊዎች በጸረ ሽብር ህግ መከሰሳቸውን፣ የ6 ጋዜጣ አሳተሚዎች በተመሳሳይ ወነጀል መከሰሳቸውን የጠቀሰው ሂማውን ራይትስ ወች፣ መንግስት ዌብሳይቶችን መዝጋቱን እንዲሁም ስልኮችን በመጥለፍ መረጃዎችን እንደሚያሰባሰብ አትቷል።
በኦሞ ሸለቆ አካባቢ በርካታ ዜጎች ያለፍላጎታቸውና ተገቢው ካሳ ሳይከፈላቸው እንደሚፈናቀሉም ድርጅቱ አስታውቋል። መንግስት ተደጋጋሚ ወቀሳና ትችት ቢደርስበትም የጸረ ሽብር ህጉንና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጀቶችን ለመቆጣጠር የወጣውን ህግ ለመቀየር ፈቃደና አለመሆኑን የጠቀሰው ሂውማን ራይትስ ወች፣ የመንግስትን የልማት እቅድ የተቹ ሰዎች እስራትና ወከባ እንደሚያጋጥማቸው አትቷል።
መንግስት ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብትን ማፈኑ በመጪው ምርጫ ላይ አሉታዊ ተጽኖ እንደሚኖረው ሌስሌ ሌፍኮው ተናግረዋል። ሂማን ራይትስ ወች በ656 ገጽ ሪፖርቱ በአለም ዙሪያ ያሉ የ90 አገራት የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን ቃኝቷል።
ኢሳት ዜና

Monday, January 26, 2015

ቢያጥቡት የማይጸዳ ዘረኛ ቡድንን ለማስወገድ ከአንድነት ጋር አንድ እንሁን !!

አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ከምስረታው እስካሁን ለወያኔ ህወሃት ቡድን ትልቅ የራስ ምታት ሆኖ ቆይቷል።በመሆኑም ድርጅቱን ለማፍረስ በተለያዩ ጊዜያት የድርጅቱን አመራሮች በማሰር፣ በመደብድብ፣ ከሀገር በማስደድ፣ በማስፈራራት እና በድርጅቱ ውስጥ ሰርጎ ገቦችን በማስረግ ያላደረገው ሙከራ አልነበረም። ሆኖም ግን አንድነት በቆራጥ አመራሮቹ ፣ አባላቶችና ደጋፊዎች ታጋድሎና መስዋእትነት እስካሁን ህልውናውን ጠብቆ ቆይቷል።
በአሁኑ ሰዓት በኢትዮጵያችን የተከሰተው አገር አቀፍ ቀውስ ህዝቡ ብሶቱን ያለምንም ፍርሃት እንዲገልጽ እያስገደደው መሆኑን የተረዳው የህወሀት ቡድን ትግሉን መርተው ከስልጣን ማማ ያወርዱኛል ብሎ የሚፈራቸውን የፖሌቲካ ድርጅቶችንና ግለሰቦችን ለማጥፋት ቆርጦ ተነስቷል። —

[ሙሉውን መግለጫ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]—

zeHabesha.com