የታላቁ ሳይቲስት የቻርል ዳርዊን 207ተኛው ልደቱ በዚህ ወር ተከብሯል። እሱ ካልው አንዱ ነገር
“ከዝርያዎች መካከል ጠንካራው አይደለም ኗሪነቱ ቀጣይነት ያለው(እማይመክነው:እማይጠፋው)። እጅግ ብልሁም አይደለም። ለለውጥ ዝግጁ የሆነው እንጂ”
ቻርልስ ዳርዊን 1809
“ከዝርያዎች መካከል ጠንካራው አይደለም ኗሪነቱ ቀጣይነት ያለው(እማይመክነው:እማይጠፋው)። እጅግ ብልሁም አይደለም። ለለውጥ ዝግጁ የሆነው እንጂ”
ቻርልስ ዳርዊን 1809
መግቢያ
ቻርል ዳርዊን የሳይንስ ብቻ ሳይሆን የፖለቲካም ሰውም የነበረ ቢሆን ኖሮ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ሁኔታ መረጃ ተሰብስቦ ቀርቦለት ምን ታስባለህ ቢባል በኦሮሞ ክፍለ አገር እየሆነ ያለው ዓመጽ የኢትዮጵያ ህዝቦችሁሉ የሚያደርጉት አገር አቀፍ ዴሞክራሲያዊ ትግል አካል ነው። ይህ እንዴት ይህ ተሰወራችሁ? ብሎን ይታዘበን ነበር እላለሁ። የሰውን ልጅ አስተሳሰብ፤ሳይንስን እንዳለ ቀየረው የሚባለውን መላምቱን ለመቅረጽ ዳርዊን የፈጀበት ጊዜ እኛ ወያኔን ስናስታምም የፈጀነውን ዘመን ያንሳል።
ለውጥ ሲመጣ እያየነው ለውጡን ወያኔ ሲያውገረግረው እኛ ግን አስተሳሰባችንንና መንገዳችንን መቀየር ካቃተን ለውጡን ወያኔ እንዲጠቀምበት አደረግን ማለት ነው።በዚህ እራሳችንንም አገራችን ኢትዮጵያንም እንበድላለን ማለት ነው። አዲስ ሁኔታ ሲከሰት ወዲያው ሁኔታውን አገናዝበን አስተሳሰባችንንም ቀይረን ዛሬ የሚጠይቀውን አቅጣጫ መቀየርን፤ማረምን፤ዝግጅትን ማድረግ እስካልቻልን ወያኔን መርታት ዳገት መሆኑ ግልጥ ነው።ጥንካሬም ብልሃትም እያለን እንዴት ወያኔ ሰነበተን? ካልጠየቅን ወያኔ አፍዝ አደንግዝ እንዳስደገመብን ያለ ነው። በኦሮሞ ክፍለ አገር እየሆነ ያለው ዓመጽ ልድገመው የኢትዮጵያ ህዝቦች ሁሉ የሚያደርጉት አገር አቀፍ ዴሞክራሲያዊ ትግል አካል ነው።
ትንታኔ
በዚህ ጽሁፍ የቻርል ዳርዊንን የአራዊትና እጽዋትን ዝርያ አመጣጥና ዝምድና ገላጭ መላምቱን የማቅረብ ዓላማ የለኝም።ከላይ የጠቀስኩት የዳርዊን አባባል የሚለግሰንን ብልሃት ለዲሞክራሲያዊ ትግላችንም ምን ይዘይድበታል ለማለት ብቻ ነው።
በወጣትነት ዘመኑ ቻርል ዳርዊን ለአምስት ዓመታት በመርከብ ዓለምን ዞሮ የጽዋትና የእንስሳትን መረጃና ናሙናም ሰብስቦ ለሃያ ዓመታት ከተመራመረ በኋላ ዝርያዎች በቀጣይነት ዘራቸው የማይጠፋው [survival] ተፈጥሮ ራሱ በደነገገው መሰረት የገጠማቸውን ነባራዊ ለውጥ ለመቀበል የተመቻቹትን ብቻ የሚመርጥ ስርዓት ስላለ መሆኑን በገናናው መላምቱ ሲያስረዳ፤ ለውጥ ለመቀበል ያቃታቸው፤መራባትም ያልሆነላቸው ዘራቸው መክሰሙንም በመላመቱ አካቶታል።
ህወሃት መሩ መንግስት ልክ እንደወታደራዊ ደርግ አዋጅ፤ህገ መንግስት፤ብሄር ገለመሌ እያለ ቀስ ብሎ ስልጣን ላይ ጉብ ሲል፤ፊቱ ለሚደቀኑ የነበሩ ተለዋጭ ሁኔታዎች መልስ እያዘጃጀ እራሱንም ለለውጥ እያመቻቸ ነበር። ዛሬም ይህንኑ ያደርጋል። እስታሁንም ለውጥ ሲመጣ ቢደናገጥም ተንገዳግዶ ይቆማል።ለለውጥ ዝግጁ መሆንና፤ፊታችን የሚከሰተውን ለውጥ ማየት እየተሳነን ህወሃትን አቸናፊ እናደርገዋለን። ይህንን ቀጥዬ ላስረዳ።
ኢትዮጵያን ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር ወያኔ ገና ከተማ ሳይገባ ማን ብርቱ ተቃውሞ እንደሚያደርግበት በመረዳት የኅይልም የፕሮፓጋንዳውንም በትር አማራው ብሄር ላይ ያሳርፍ ነበር።ህወሃት ጋር የተደለሉ ኦሮሞዎች ሎሎችም እየተባበሩ።ከአማራውም ከሌሎች ብሄሮችም ተጨምረው አድር ባዮችን በጥቅም አሰልፎ ሲያበቃ የራሱን በፖለቲካ ስልጣን መደርጀትን የዝምድና ሀረግ በማድረግ ሰንብቶበታል። ይህ ዛሬም ያለ ዝምድና ነው።ይህን ዝምድና ስር ነቀል ለውጥ ብቻ የሚሽረው ነውና ህወሃት እስታለ ደግሞ ይቀጥላል።ህወሃትን ዲሞክራሲያዊው ትግል በድል ሲሽረው ወያኔ ጋር አብሮ ታሪክና ትዝብት ይሆናል። ባጭሩ ወያኔ ዝግጅት አድርጎ ሲገባ ህዝባዊ ዴሞክራሲያዊ ሀይሎች አልተዘጋጁም ነበር።ይሄው ሃያ አምስት ዓመታ እየተቆጠሩ ነው።
እንዳአሁኑ የወጣት ተማሪዎች እንቅስቃሴ የኦሮሞ ብሄረሰብ በብዛት በሚኖርባቸው የኢትዮጵያ ክፍላተ አገር እንደሚካሄደው በሌሎቹም ቦታዎች እየተነሱ ተራ በተራ መመታታቸውን አይተናል።ህወሃት አገር አቀፍ እንዳይባልበት እጅግ ሲጥር የመጣውን ለው የሁላችን የጋራ ነው ለማለት ተስኖን በመደናገር ራሱ ህወሃት ያለው ደግመን [ትቀብለን] አመጹን “የኦሮሞ”፤ “የአማራ” እናደርገዋለን።ባጭሩ ቻርልስ ዳርዊን እንደሚለው ሀይል ቢኖረንም ለውጡን ለመጠቀም ራሱን ያመቻቸው ህወሃት ሆኖ እናገኘዋለን።
በኦሮሞ ክፍለ አገር ዛሬ ተቀጣጥሎ እየነደደ ያለው ዓመጽ እንዴት ተከሰተ?የህዝባዊ ብሶቱ መነሻ ምንድን ነው?በሌሎች የኢትዮጵያ ክፍላተ አገራት ከተነሱት ዓመጾች በምን ይመሳሰላል?እንዴት ሊራመድ ይችላል?ወያኔን ለማንበርከክ ምን ቀጥሎ ምን ይደረግ እንደማለት ህወሃት ለመጣው ለውጥ የሰጠውን ስያሜ ውጠን “የኦሮሞ ክልል” የዚያ ክልል የሚል ታርጋ እንለጥፍበታለን።ለህወሃትም የሌለውን ብላተኛነት አክለንለት ከናካቴው አመጹን ወያኔ በውስጥ እጅ ሆን ብሎ በራሱ ሰዎች እንዳስነሳው የምናስብም አለን። የተንኮል ቅንብር (Conspiracy Theory) ድረስ የምንሄድና ወጣቱ በደሙ የከፈለበትን መና ለማድረግና ህወሃትም ለመርታት አስቸጋራ መስሎ እንዲታይ ያለማስተዋል እንናገራለን።ህወሃት ጠንካራ አይደለም።ብልሃትም የለውም።የለት ተለትዋን ለማድረግ ግን ጮሌ ነው። እስታሁን በራሱ ላይ ህዝባዊ አመጽ ሆን ብሎ የሚዶልት አምባገነን ታይቶ የሚታወቅ አይመስለኝም።ህወሃት ግን የተፈጠረውን ሁኔታ ሊጠቀምበት የማያደርገው የለም ማለት ይቻላል።በግልጹ ለመናገር አማራው ኦሮሞውን፤ኦሮሞው አማራውን እንዲጠላውና እንዲጠራጠረው በመሆኑ የህወሃት ፍላጎት እደተመኘው የምንሆንለት እራሳችኑ ነን።ተመቸነው ልበል ወጣቶች እንደሚሉት ?ለውጥን ፈርተን መለወጥ አቅቶን እንዴት ወያኔን ለማሰናበት እንችላለን?
ነገ የአማራው ህዝብ በብዛት በሚኖርበት ክፍለ አገር አመጽ ቢቀጣጠል።የጋምቤላውና የአፋሩ እንደቀድሞው ቦግ ሲል የህወሃት መሩን መንግስት መግለጫ ተቀብለን የምናስተጋባ ከሆነ ብልሃትም ጉልበትም የኛ ቢሆንም ወያኔ የለመደውን ግዜያዊ ድል አግኝቶ ቀጠለ ማለት ነውና፤ ሲሆን ለውጥ ሳይመጣ ቀድመን እናስላ ካልሆነ ለውጡ፤አመጽ ሲከሰት ሌላ ስም ሳይሆን አገር አቀፍ ዴሞክራሲያዊ ትግል መሆኑን ኢትዮጵያ አገሬ የምንል ይህን ስያሜ እንጂ የወያኔን አናስተጋባ።ሌላ ምሳሌ ”ኢትዮጵያ ትፈራርሳለች” ሲል የወያኔ ተረት ተረት “ወያኔ ስንት ቦታ ተሰንጥቆ ይፈርሳል ?” ብለን ይህን ሂደት ለማፋጠን ምን ይደረግ እንበል።ዛሬ ኢትዮጵያ ለለውጥ ዝግጁ ናት የምሁራንዋ ዝግመት እንጂ !” ይህን እናስብበት::
የኢትዮጵያ ህዝቦች የሚያደርጉት አገር አቀፍ ዴሞክራሲያዊ ትግል ያቸንፋል!
የፖለቲካ መሪዎች አሁኑኑ ይፈቱ!
የሃይማኖት መሪዎች አሁኑኑ ይፈቱ!
የታሰሩ ጋዜጠኞች አሁኑኑ ይፈቱ!
ለወጣቶች ግድያ ህወሃት እንጂ ማንም ተጠያቂ አይደለም !
ቻርል ዳርዊን የሳይንስ ብቻ ሳይሆን የፖለቲካም ሰውም የነበረ ቢሆን ኖሮ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ሁኔታ መረጃ ተሰብስቦ ቀርቦለት ምን ታስባለህ ቢባል በኦሮሞ ክፍለ አገር እየሆነ ያለው ዓመጽ የኢትዮጵያ ህዝቦችሁሉ የሚያደርጉት አገር አቀፍ ዴሞክራሲያዊ ትግል አካል ነው። ይህ እንዴት ይህ ተሰወራችሁ? ብሎን ይታዘበን ነበር እላለሁ። የሰውን ልጅ አስተሳሰብ፤ሳይንስን እንዳለ ቀየረው የሚባለውን መላምቱን ለመቅረጽ ዳርዊን የፈጀበት ጊዜ እኛ ወያኔን ስናስታምም የፈጀነውን ዘመን ያንሳል።
ለውጥ ሲመጣ እያየነው ለውጡን ወያኔ ሲያውገረግረው እኛ ግን አስተሳሰባችንንና መንገዳችንን መቀየር ካቃተን ለውጡን ወያኔ እንዲጠቀምበት አደረግን ማለት ነው።በዚህ እራሳችንንም አገራችን ኢትዮጵያንም እንበድላለን ማለት ነው። አዲስ ሁኔታ ሲከሰት ወዲያው ሁኔታውን አገናዝበን አስተሳሰባችንንም ቀይረን ዛሬ የሚጠይቀውን አቅጣጫ መቀየርን፤ማረምን፤ዝግጅትን ማድረግ እስካልቻልን ወያኔን መርታት ዳገት መሆኑ ግልጥ ነው።ጥንካሬም ብልሃትም እያለን እንዴት ወያኔ ሰነበተን? ካልጠየቅን ወያኔ አፍዝ አደንግዝ እንዳስደገመብን ያለ ነው። በኦሮሞ ክፍለ አገር እየሆነ ያለው ዓመጽ ልድገመው የኢትዮጵያ ህዝቦች ሁሉ የሚያደርጉት አገር አቀፍ ዴሞክራሲያዊ ትግል አካል ነው።
ትንታኔ
በዚህ ጽሁፍ የቻርል ዳርዊንን የአራዊትና እጽዋትን ዝርያ አመጣጥና ዝምድና ገላጭ መላምቱን የማቅረብ ዓላማ የለኝም።ከላይ የጠቀስኩት የዳርዊን አባባል የሚለግሰንን ብልሃት ለዲሞክራሲያዊ ትግላችንም ምን ይዘይድበታል ለማለት ብቻ ነው።
በወጣትነት ዘመኑ ቻርል ዳርዊን ለአምስት ዓመታት በመርከብ ዓለምን ዞሮ የጽዋትና የእንስሳትን መረጃና ናሙናም ሰብስቦ ለሃያ ዓመታት ከተመራመረ በኋላ ዝርያዎች በቀጣይነት ዘራቸው የማይጠፋው [survival] ተፈጥሮ ራሱ በደነገገው መሰረት የገጠማቸውን ነባራዊ ለውጥ ለመቀበል የተመቻቹትን ብቻ የሚመርጥ ስርዓት ስላለ መሆኑን በገናናው መላምቱ ሲያስረዳ፤ ለውጥ ለመቀበል ያቃታቸው፤መራባትም ያልሆነላቸው ዘራቸው መክሰሙንም በመላመቱ አካቶታል።
ህወሃት መሩ መንግስት ልክ እንደወታደራዊ ደርግ አዋጅ፤ህገ መንግስት፤ብሄር ገለመሌ እያለ ቀስ ብሎ ስልጣን ላይ ጉብ ሲል፤ፊቱ ለሚደቀኑ የነበሩ ተለዋጭ ሁኔታዎች መልስ እያዘጃጀ እራሱንም ለለውጥ እያመቻቸ ነበር። ዛሬም ይህንኑ ያደርጋል። እስታሁንም ለውጥ ሲመጣ ቢደናገጥም ተንገዳግዶ ይቆማል።ለለውጥ ዝግጁ መሆንና፤ፊታችን የሚከሰተውን ለውጥ ማየት እየተሳነን ህወሃትን አቸናፊ እናደርገዋለን። ይህንን ቀጥዬ ላስረዳ።
ኢትዮጵያን ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር ወያኔ ገና ከተማ ሳይገባ ማን ብርቱ ተቃውሞ እንደሚያደርግበት በመረዳት የኅይልም የፕሮፓጋንዳውንም በትር አማራው ብሄር ላይ ያሳርፍ ነበር።ህወሃት ጋር የተደለሉ ኦሮሞዎች ሎሎችም እየተባበሩ።ከአማራውም ከሌሎች ብሄሮችም ተጨምረው አድር ባዮችን በጥቅም አሰልፎ ሲያበቃ የራሱን በፖለቲካ ስልጣን መደርጀትን የዝምድና ሀረግ በማድረግ ሰንብቶበታል። ይህ ዛሬም ያለ ዝምድና ነው።ይህን ዝምድና ስር ነቀል ለውጥ ብቻ የሚሽረው ነውና ህወሃት እስታለ ደግሞ ይቀጥላል።ህወሃትን ዲሞክራሲያዊው ትግል በድል ሲሽረው ወያኔ ጋር አብሮ ታሪክና ትዝብት ይሆናል። ባጭሩ ወያኔ ዝግጅት አድርጎ ሲገባ ህዝባዊ ዴሞክራሲያዊ ሀይሎች አልተዘጋጁም ነበር።ይሄው ሃያ አምስት ዓመታ እየተቆጠሩ ነው።
እንዳአሁኑ የወጣት ተማሪዎች እንቅስቃሴ የኦሮሞ ብሄረሰብ በብዛት በሚኖርባቸው የኢትዮጵያ ክፍላተ አገር እንደሚካሄደው በሌሎቹም ቦታዎች እየተነሱ ተራ በተራ መመታታቸውን አይተናል።ህወሃት አገር አቀፍ እንዳይባልበት እጅግ ሲጥር የመጣውን ለው የሁላችን የጋራ ነው ለማለት ተስኖን በመደናገር ራሱ ህወሃት ያለው ደግመን [ትቀብለን] አመጹን “የኦሮሞ”፤ “የአማራ” እናደርገዋለን።ባጭሩ ቻርልስ ዳርዊን እንደሚለው ሀይል ቢኖረንም ለውጡን ለመጠቀም ራሱን ያመቻቸው ህወሃት ሆኖ እናገኘዋለን።
በኦሮሞ ክፍለ አገር ዛሬ ተቀጣጥሎ እየነደደ ያለው ዓመጽ እንዴት ተከሰተ?የህዝባዊ ብሶቱ መነሻ ምንድን ነው?በሌሎች የኢትዮጵያ ክፍላተ አገራት ከተነሱት ዓመጾች በምን ይመሳሰላል?እንዴት ሊራመድ ይችላል?ወያኔን ለማንበርከክ ምን ቀጥሎ ምን ይደረግ እንደማለት ህወሃት ለመጣው ለውጥ የሰጠውን ስያሜ ውጠን “የኦሮሞ ክልል” የዚያ ክልል የሚል ታርጋ እንለጥፍበታለን።ለህወሃትም የሌለውን ብላተኛነት አክለንለት ከናካቴው አመጹን ወያኔ በውስጥ እጅ ሆን ብሎ በራሱ ሰዎች እንዳስነሳው የምናስብም አለን። የተንኮል ቅንብር (Conspiracy Theory) ድረስ የምንሄድና ወጣቱ በደሙ የከፈለበትን መና ለማድረግና ህወሃትም ለመርታት አስቸጋራ መስሎ እንዲታይ ያለማስተዋል እንናገራለን።ህወሃት ጠንካራ አይደለም።ብልሃትም የለውም።የለት ተለትዋን ለማድረግ ግን ጮሌ ነው። እስታሁን በራሱ ላይ ህዝባዊ አመጽ ሆን ብሎ የሚዶልት አምባገነን ታይቶ የሚታወቅ አይመስለኝም።ህወሃት ግን የተፈጠረውን ሁኔታ ሊጠቀምበት የማያደርገው የለም ማለት ይቻላል።በግልጹ ለመናገር አማራው ኦሮሞውን፤ኦሮሞው አማራውን እንዲጠላውና እንዲጠራጠረው በመሆኑ የህወሃት ፍላጎት እደተመኘው የምንሆንለት እራሳችኑ ነን።ተመቸነው ልበል ወጣቶች እንደሚሉት ?ለውጥን ፈርተን መለወጥ አቅቶን እንዴት ወያኔን ለማሰናበት እንችላለን?
ነገ የአማራው ህዝብ በብዛት በሚኖርበት ክፍለ አገር አመጽ ቢቀጣጠል።የጋምቤላውና የአፋሩ እንደቀድሞው ቦግ ሲል የህወሃት መሩን መንግስት መግለጫ ተቀብለን የምናስተጋባ ከሆነ ብልሃትም ጉልበትም የኛ ቢሆንም ወያኔ የለመደውን ግዜያዊ ድል አግኝቶ ቀጠለ ማለት ነውና፤ ሲሆን ለውጥ ሳይመጣ ቀድመን እናስላ ካልሆነ ለውጡ፤አመጽ ሲከሰት ሌላ ስም ሳይሆን አገር አቀፍ ዴሞክራሲያዊ ትግል መሆኑን ኢትዮጵያ አገሬ የምንል ይህን ስያሜ እንጂ የወያኔን አናስተጋባ።ሌላ ምሳሌ ”ኢትዮጵያ ትፈራርሳለች” ሲል የወያኔ ተረት ተረት “ወያኔ ስንት ቦታ ተሰንጥቆ ይፈርሳል ?” ብለን ይህን ሂደት ለማፋጠን ምን ይደረግ እንበል።ዛሬ ኢትዮጵያ ለለውጥ ዝግጁ ናት የምሁራንዋ ዝግመት እንጂ !” ይህን እናስብበት::
የኢትዮጵያ ህዝቦች የሚያደርጉት አገር አቀፍ ዴሞክራሲያዊ ትግል ያቸንፋል!
የፖለቲካ መሪዎች አሁኑኑ ይፈቱ!
የሃይማኖት መሪዎች አሁኑኑ ይፈቱ!
የታሰሩ ጋዜጠኞች አሁኑኑ ይፈቱ!
ለወጣቶች ግድያ ህወሃት እንጂ ማንም ተጠያቂ አይደለም !
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!