Wednesday, April 22, 2015

በአዲስ አበባ አንድ ኢትዮጵያዊ ራሱን አቃጠለ

ሚያዝያ ፲፩(አስራ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ዛሬ ሚያዚያ 12 ፣ 2007ዓም ኡራኤል አካባቢ አንድ ኢትዮጵያዊ ቤንዚን በራሱ ላይ አርከፍክፎ የተወሰነ የሰውነት ክፍሉ ከተቃጠለ በሁዋላ በህዝብና በፖሊስ እርዳታ ሊተርፍ ችሎአል።
የአይን እማኞች ግለሰቡ ሙሉ ልብስ የለበሰ እና ጥሩ የሰውነት ቁመና  ያለው መሆኑን ተናግረዋል።  ፖሊሶችም ግለሰቡን ወደ ስድሰተኛ ፖሊስ ጣቢያ ወስደውታል
ዘግይቶ በመጣው መረጃ ደግሞ ግለሰቡ የመንግስት ሰራተኛና ከስራ ከወጣ በሁዋላ ድርጊቱን መፈጸሙ ታውቋል።

No comments:

Post a Comment