Thursday, December 4, 2014

ፀረ-ኢትዮጵያዊውና ዘረኛው ወያኔ በኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ስም አይነግድም!

ኮለምበስ፣ ኦሃዮ – ፀረ-ኢትዮጵያዊውና ዘረኛው ወያኔ በኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ስም አይነግድም!

December 3, 2014
መርሐ አንድነት የኢትዮጵያውያን ሲቪክ ማህበር በኮለምበስ፣ ኦሃዮ

Click here for PDF

የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ቅጥረኛ የሆነው ፀረ-ኢትዮጵያዊውና ቅኝ-ገዥው ወያኔ ባሕር ማዶ ተሻግሮ በሃገረ አሜሪካ ኮለምበስ ኦሃዮ “በስሜን አሜሪካ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች Tigray People Front, TPLFየባሕል ክብረ በዓል” በሚል ስም እሑድ ኅዳር 28 ቀን 2007 ዓ/ም ( Sunday, December 7, 2014 ) ከቀኑ 1:00pm ጀምሮ በሃያት ረጀንሲ ሆቴል (Hyatt Regency Hotel @ 350 North High Street, Columbus, OH 43215) ለማክበር በዝግጅት ላይ ይገኛል። ለዚህ በዓል መሰናዶ፤ ዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው የወያኔ ኢምባሲ የበላይ መሪ በመሆን፤ በአካባቢያችን ያሉትን የለየላቸው ከሃዲዎችና የባንዳ ልጆችና የልጅ ልጆች በአስተባባሪነት በማሰለፍ ነው።
ለአለፉት 23 ዓመታት ሃገራችንን ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት ቀንበር ሥር በማዋል የፖለቲካውን ኃይል፣ የኢኮኖሚውን ዘርፍ፣ የማህበራዊ አውታሩን፤ የወታደራዊ ተቋሙንና የደኅንነቱን መረብ በሙሉ የተቆጣጠረው ፀረ-ኢትዮጵያዊውና ዘረኛው ወያኔ የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች የባሕል ክብረ በዓል ለማክበር የኅሊና ብቃት አለው ወይ?
1. ማን ሆነና ነው ብሔር ብሔረሰቦችን እርስ በእርሳቸው ለያይቶና ከፋፍሎ የሚያስጨራርሰው?
2. ማን ሆነና ነው ብሔር ብሔረሰቦችን በሃይማኖት ከፋፍሎ የሚያወዛግበውና የሚያዋጋው?
3. ማን ሆነና ነው ወገናችን አማራውን፣ ኦሮሞውን፣ ሱማሊውን፣ አኝዋኩን፣ አፋሩን ወዘተ… እየጨፈጨፈ የምድር ሲዖል እያሳየ የዘር ማጽዳት ዘመቻ የሚያካሂደው?
4. ማን ሆነና ነው በቅርብ ጊዜ በመቶ ሺህዎች የሚቆጠሩትን አማራዎች ሃብትና ንብረታቸውን እያዘረፈ፣ ቤታቸውን እያቃጠለና እየገደለ ከሃገራችን ውጡ እያለ ከጉራፈርዳ፣ ከቤኒሻንጉል-ጉሙዝ፣ ከጋምቤላ ወዘተ.. ያፈናቀለውና ያባረረው?
5. ማን ሆነና ነው ለቀንደኛ ደንበር-ዘለል ተስፋፊና ዘራፊ ሃገሮችና ኩባኒያዎች ለም ድንግል መሬቶቻችንን በመሸጥ በመቶ ሺህዎች የሚገመቱትን የደቡብ ኢትዮጵያና የጋምቤላ ብሔር ብሔረሰቦችን ከቀያቸው በማፈናቀል ሃገራችንን ለከፍተኛ አደጋ ያጋለጠው?
6. ማን ሆነና ነው ከፍተኛ የተፈጥሮ ሃብት ክምችት ያለውን የሃገራችንን ዳር-ድንበር ለም መሬት ለሱዳን የሽጠው?
7. ማን ሆነና ነው የብሔር ብሔረሰቦችን የጋራ ማህበራዊና ባሕላዊ እሴቶቻቸውንና አብሮነታቸውን የሸረሸረውና ለማጥፋት ተንኮልንና ሴራ የሚሸርበው?
8. ማን ሆነና ነው ርካሽና አስነዋሪ የባእድ ባሕሎች በብሔር ብሔረሰቦቻችን ላይ እንዲስፋፋ ያደረገው?
9. ማን ሆነና ነው በሺህዎች የሚቆጠሩትን ወገኖቻችንን በብሔር ማንነታቸው እየወነጀለ ወደ ወህኒ የሚወረውረው?
10. ማን ሆነና ነው ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን ለማጥፋት ቁጥር አንድ አጀንዳውን አንግቦ ከደደቢት፣ ትግራይ የተነሳው?
ይህን ሁሉ ግድያ፣ ግፍ፣ መከራ፣ በደልና ሰቆቃ በኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ላይ የሚፈጽመው ፀረ-ኢትዮጵያዊውና ዘረኛው ወያኔ አይደለምን? አዎ ነው። ስለዚህ፣ እኛ የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ልጆችም በነፍስ ገዳያችን ድግስ አንገኝም። በታላቅ ቆራጥነት በነፍስ ገዳያችን ላይ ሕዝባዊ ትግሉን እናጧጥፋለን እንጅ።
ስለዚህ፣ በኮለምበስ ከተማና በአካባቢው ከተሞች፤ እንዲሁም በአጎራባች ስቴቶች የምትገኙ ሃገር-ወዳድ ኢትዮጵያውያን፤ ዘረኛውና ጎጠኛው ወያኔ እሑድ ኅዳር 28 ቀን 2007 ዓ/ም ( Sunday, December 7, 2014 ) ከቀኑ 1:00pm ጀምሮ ኮለምበስ ኦሃዮ በሚገኘው ሃያት ረጀንሲ ሆቴል ( Hyatt Regency Hotel @ 350 North High Street, Columbus, OH 43215) በጠራው ስብሰባ ላይ እንዳትገኙ፤ ወራሪውንና ፋሽስቱን ወያኔ ሲፋለሙ በታላቅ ጀግንነት በተሰውት የአማራ፣ የኦሮሞ፣ የሱማሊ፣ የአኝዋክ፣ የአፋር ወዘተ… የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ልጆች ስም ሃገራዊ ጥርያችንን እናስተላልፋለን። ሆኖም ግን፣ ይህን ሕዝባዊ ጥሪ ባለመቀበል በዚህ የወያኔ ስብሰባ የምትገቡ፤ የተሰውትን የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ልጆች አጥንት ረግጣችሁ እንደገባችሁ እወቁት። እኛም እንደ እናንተ ያለውን ሆድ-አደር ባንዳ ለኢትዮጵያ ሕዝብ በይፋ የምናጋልጥ መሆኑን ከወዲሁ በጥብቅ እናሳስባለን።
የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች እኩልነት በትግላችን ይመሠረታል!
ፀረ-ኢትዮጵያዊውና ቅኝ-ገዥው ወያኔ በሕዝባዊ ክንዳችን ይደመሰሳል!
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!
መርሐ አንድነት የኢትዮጵያውያን


    ሲቪክ ማህበር በኮለምበስ፣ ኦሃዮ

    No comments:

    Post a Comment