በበርካታ ኢትዮጵያውያን ብርቱ ትግል ቢቢሲ ራድዮ የኦሮሚኛ ቋንቋ ሥርጭት ለመጀመር ፈቃደኛ መሆኑ ተሰማ -
(ዘ-ሐበሻ) ቢቢሲ በመካከለኛና በአጭር ሞገድ የትግርኛና የአማርኛ ቋንቋ የራድዮ ስርጭቶችን ወደ ኤትዮጵያና ኤርትራ ለመጀመር እቅዱን ካወጣ በኋላ በርካታ ኢትዮጵያውያን ከአማርኛ እና ከትግርኛ ቋንቋ በተጭማሪ የኦሮሚኛ ፕሮግራምም እንዲጀመር ባደረጉት ሰፊ ትግል የዓለማችን ትልቁ የመረጃ ተቋም የሕዝቡን ጥያቄ መቀበሉን ምንጮች አስታወቁ:: ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮጵያ ወዳጆች በዓለም አቀፍ ደረጃ የፊርማ ማሰባሰብ በማህበራዊ ድረገጾች በማድረግ ቢቢሲ የኦሮሚኛ ቋንቋ የራድዮ ስርጭትም እንዲጀምር ግፊት ያደረጉ ሲሆን ተቋሙም በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ የሕዝብ ፊርማዎችን ከተመለከተ በኋላ ጥያቄውን ተቀብሏል ተብሏል:: ቢቢሲ በይፋ ይህንን ጥያቄ በቅርቡ ለሕዝብ ያቀርበዋል ያሉት ምንጮች በአማርኛ; በኦሮሚኛ እና በትግርኛ ቋንቋዎች የቢቢሲ ራድዮ ዝግጅቶች በመካከለኛውና በአጭር ሞገድ ለመቅረብ መወሰኑ እንደ ትልቅ ድል ይቆጠራል ብለዋል:: ቢቢሲ የኦሮሚኛ ቋንቋን እንዲጀምር ግፊት ለማድረግ በተደረገው የፊርማ ማሰባሰብ እንቅስቃሴ ውስጥ በአንድነት የተንቀሳቀሱ ኃይሎች በሌሎች ሃገራዊ ጉዳዮች ላይም እንዲሁ በሕብረት ለውጥ የሚያመጡ ጥረቶችን በጋራ እንዲሰሩ ከሕዝብ ጥሪ ቀርቧል:: -
No comments:
Post a Comment