መምህር ግርማ በተጠረጠሩበት የግድያ ክስ የሟች አስከሬን በድጋሚ እንዲመረመር ታዘዘ
ዘ-ሐበሻ) መምህር ግርማ ወንድሙ ዛሬ ፍርድ ቤት ቀረቡ:: ፖሊስ በመምህሩ ላይ ከግድያ ወንጀል ጋር በተያያዘ ያቀረበው ክስ የተሰማ ሲሆን የተከሰሱበት አስከሬን ጉዳይንም ፍርድ ቤቱ ተመለከተው:: ፍርድ ቤቱ እንዳዘዘው መምህር ግርማ በተጠረጠሩበት የግድያ ክስ አስከሬኑ በድጋሚ እንዲመረመር ፍርድ ቤቱ ማዘዙን የዘ-ሐበሻ ምንጮች አስታውቀዋል:: የአስከሬን ምርመራው ተጠናቆም መምህር ግርማ ታህሳስ 4, 2008 ዓ.ም ፍርድ ቤት ተመልሰው እንዲቀርቡ ታዟል:: በመምህር ግርማ ላይ ከግድያ ወንጀል ጋር በተያያዘ ክስ ለመመስረት ዝግጅት እንዳለ ከአንድ ወር በፊት ዘ-ሐበሻ ቀድማ ምንጮቿን ጠቅሳ መዘገቧ አይዘነጋም:: - See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/48603#sthash.tGkwU6uf.dpuf
No comments:
Post a Comment